የሶማሊላንድ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ፕሬዝደንታዊ ምርጫውን አሸነፉ

Date:

የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ተቃዋሚ መሪ ባለፈው ሳምንት የተካሄደውን ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ማሸነፋቸውን የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን በዛሬው እለት ይፋ ማድረጉን ኤፒ ዘግቧል።

የዋና ተቃዋሚው ዋዳኒ ፓርቲ መሪ አብዲራህማን ሞሀመድ አብዱላሂ ከ50 በመቶ በላይ ድምጽ ማግኘት ችለዋል።

ለሰባት አመታት ሶማሊላንድን የመሩት የቀድሞው ገዥ ፓርቲ ኩልምዬ መሪ ሙሴ ቢሂ አብዲ 30 በመቶ ድምጽ በማግኘት ሁለተኛ ሆነዋል።

ምርጫው በበጀት እጥረት እና በሌሎች ምክንያቶች ከ2022 ወዲህ ለሁለት ጊዜ መራዘሙ ይታወሳል።

 ግጭት እየተካሄደ በነበረበት በ1991 ከሶማሊያ የተገነጠለችው ራስ ገዟ ሶማሊላንድ አለምአቀፍ እውቅና ባይኖራትም የራሷ መንግስት፣ መገበያያ ገንዝብ እና የራሷ የጸጥታ መዋቅር አላት። ሶማሊላንድ ከሶማሊያ ይልቅ ለአመታት የተረጋጋች ሆኗ ቆይታለች።

ሶማሊሊንድ ባለፈው የፈረንጆቹ አዲስ አመት ከጎረቤት ኢትዮጵያ ጋር የተፈራረመችው የወደብ ስምምነት ሉአላዊነቴ ተጥሷል በምትለው ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ መካከል ውጥረት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የክሪፕቶ ሥራ ፈጣሪው የ15 ዓመት እስር ተፈረደበት

የቀድሞው የክሪፕቶከረንሲ ሥራ ፈጣሪ ተሰውሯል ከተባለ 40 ቢሊየን ዶላር...

5ኛው የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል ተካሄደ

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አዘጋጅነት በየዓመቱ በፈረንጆቹ ታኅሣሥ...

የንግድ ሚኒስቴር 13 ምርቶችን በመነሻ ሀገር የጥራት ማረጋገጫ (PVoC) እንዲያገኙ ወሰነ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፣ በሀገር...

ገዳ ባንክ ከ444 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፤ ባንኮች የተከፈለ ካፒታላቸውን በ2018 ዓ.ም...