የሶማሊላንድ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ፕሬዝደንታዊ ምርጫውን አሸነፉ

Date:

የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ተቃዋሚ መሪ ባለፈው ሳምንት የተካሄደውን ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ማሸነፋቸውን የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን በዛሬው እለት ይፋ ማድረጉን ኤፒ ዘግቧል።

የዋና ተቃዋሚው ዋዳኒ ፓርቲ መሪ አብዲራህማን ሞሀመድ አብዱላሂ ከ50 በመቶ በላይ ድምጽ ማግኘት ችለዋል።

ለሰባት አመታት ሶማሊላንድን የመሩት የቀድሞው ገዥ ፓርቲ ኩልምዬ መሪ ሙሴ ቢሂ አብዲ 30 በመቶ ድምጽ በማግኘት ሁለተኛ ሆነዋል።

ምርጫው በበጀት እጥረት እና በሌሎች ምክንያቶች ከ2022 ወዲህ ለሁለት ጊዜ መራዘሙ ይታወሳል።

 ግጭት እየተካሄደ በነበረበት በ1991 ከሶማሊያ የተገነጠለችው ራስ ገዟ ሶማሊላንድ አለምአቀፍ እውቅና ባይኖራትም የራሷ መንግስት፣ መገበያያ ገንዝብ እና የራሷ የጸጥታ መዋቅር አላት። ሶማሊላንድ ከሶማሊያ ይልቅ ለአመታት የተረጋጋች ሆኗ ቆይታለች።

ሶማሊሊንድ ባለፈው የፈረንጆቹ አዲስ አመት ከጎረቤት ኢትዮጵያ ጋር የተፈራረመችው የወደብ ስምምነት ሉአላዊነቴ ተጥሷል በምትለው ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ መካከል ውጥረት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...