ፊርማው በማኖር የማይረሳ መታሰቢያ አበርክቶለታል
የቀድሞው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንና የአርሰናል እግር ኳስ ኮከብ ባካሪ ሳኛ በኢትዮጵያ እያደረገ ባለው ቆይታ፣ ከታላቁ አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ ጋር በኃይሌ ግራንድ አዲስ ሆቴል ተገናኝቷል።
ሁለቱ ስፖርተኞች በነበራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን ቡና አብረው ከመጠጣታቸው ባለፈ፣ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።
ለብዙ ምዕራባውያን የዓለም ስፖርተኞች ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴን ማግኘት እንደ ትልቅ ዕድልና ክብር የሚቆጠር ሲሆን፤ ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴም ለባካሪ ሳኛ የራሱን ፊርማ (Autograph) በማኖር የማይረሳ መታሰቢያ አበርክቶለታል።
ይህም ጀግናው አትሌታችን ኃይሌ ገ/ሥላሴ በዓለም መድረክ ያለውን የላቀ ቦታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ክስተት ነው፡፡
Haile Hotels and Resorts
