የቀድሞው የአርሰናል እግር ኳስ ኮከብና አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ

Date:

ፊርማው በማኖር የማይረሳ መታሰቢያ አበርክቶለታል

የቀድሞው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንና የአርሰናል እግር ኳስ ኮከብ ባካሪ ሳኛ በኢትዮጵያ እያደረገ ባለው ቆይታ፣ ከታላቁ አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ ጋር በኃይሌ ግራንድ አዲስ ሆቴል ተገናኝቷል።

ሁለቱ ስፖርተኞች በነበራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን ቡና አብረው ከመጠጣታቸው ባለፈ፣ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።

ለብዙ ምዕራባውያን የዓለም ስፖርተኞች ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴን ማግኘት እንደ ትልቅ ዕድልና ክብር የሚቆጠር ሲሆን፤ ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴም ለባካሪ ሳኛ የራሱን ፊርማ (Autograph) በማኖር የማይረሳ መታሰቢያ አበርክቶለታል።

ይህም ጀግናው አትሌታችን ኃይሌ ገ/ሥላሴ በዓለም መድረክ ያለውን የላቀ ቦታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ክስተት ነው፡፡

Haile Hotels and Resorts

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...