” የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለተፈጠሩት ችግሮች መፍትሔ በመስጠት ሐዋርያዊ አደራውን እንዲወጣ በልጅነት መንፈስ ዝቅ ብለን እንማፀናለን! ” የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት

Date:

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም በተደረገ ስብሰባ የዘንድሮ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በርካታ ሥር ነቀል ለውጦችን ማምጣት የሚችል ፤ ለነገይቱ የቤተክርስቲያን ተረካቢ ወጣቶች መሰረት የጣለ እንዲሆን ያለመ ምክረ ሐሳብ ተወያይቶ ማቅረቡን አስታውቋል።

ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ቀርበው መፍትሔ እንዲሰጥባቸው ከቀረቡት ውስጥ ፦ የቤተክርስቲያንን ሲኖዶሳዊ ልዕልና እና አንድነትን ማስጠበቅ ፣ የቤተክርስቲያንን አስተዳደራዊ ችግሮችን በመለየት መፍታት ፣ የሥነ ምግባር ግድፈት እና የቀኖና ጥሰት መበራከት ፣ በሀገራዊና ዓለም አቀፍ ጉዳይ ላይ የሚኖሩ ተሳትፎዎች ዋና ዋና ጉዳዮች ስለመሆናቸው በመልእክቱ ተላልፏል።

ሐሰተኛ የሆኑ የኑፋቄ ትምህርቶች ፣ በሰላም እጦት የሚገኙ አህጉረ ስብከቶች ፣ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሚና ፣የሀብት ብክነት ፣ ዘመኑን የዋጀ የአሠራር መንገድ መዘርጋት ፣ መንፈሳዊ አገልግሎት ላይ የሚስተዋሉ እና አፈንግጠው የወጡ ሥርዓቶች ፣ በከተማ ልማት መስፋፋት የምእመናን ከአምልኮ ሥፍራ መራቅ ፣ ሀገራዊ የችግር አፈታት መንገዶች ላይ ምልዓተ ጉባኤውም በስፋት እንዲወያይ አንድነቱ በዝርዝር ካስቀመጣቸው ሐሳቦች መሐል ይገኙበታል።

እነዚህን እና ሌሎች የውይይት ሐሳቦችን በዝርዝር በማቅረብ ” የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መፍትሔ በመስጠት ሐዋርያዊ አደራውን እንዲወጣ በልጅነት መንፈስ ዝቅ ብለን እንማፀናለን! ” በማለት አንድነቱ መልእክቱን አጋርቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...