የብርቱካን ሚደቅሳ “መመለስ” መጽሐፍ ተመረቀ።

Date:

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በአቋም ጽናትና በአመራር ብቃቷ በምትታወቀው ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ የተዘጋጀው “መመለስ፦ ቦጌ ትውስታዎቼ” የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ መጽሐፍ በርካታ እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተመርቋል።

ብርቱካን ሚደቅሳ በዚህ መጽሐፏ ታሪኳን የተረከችበት፣ ልምዷን ያካፈለችበት፣አስገራሚውን የሕይወት ታሪኳን በመጽሐፍ መልክ እንዳዘጋጀች በመድረኩ ተገልጿል።

በምረቃ ሥነሥርዓቱ ላይ የመጽሐፉ አርታዒያን መሠረት አበጀ፥ይኩኖአምላክ መዝገቡ ንግግር አድርገዋል።

አበበ ባልቻ እና ቆንጂት ስዩም ከመጽሐፉ የውስጥ ገፆች ለታዳሚው አንብበዋል።

በሶሊያና ሽመልስ አወያይነት መዓዛ ወርቁ፣ ሕይወት ተፈራ፣ ቴዎድሮስ አጥላውና ዳዊት ብርሃኑ ሃሳቦቻቸውን አጋርተዋል።

“መመለስ: ቦጌ ትውስታዎቼ” መጽሐፍ በ37 ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን በ292 ገፆች ተቀንብቦ ለንባብ በቅቷል። በቅርቡ በተለያዩ የመጽሐፍ መደብሮች በኩል ለገበያ እንደሚቀርብም ተገልጿል።

የዚህ ፕሮግራም ብቸኛ የሚዲያ አጋር አርትስ ቴሌቪዥን ሲሆን ሙሉ የምረቃ ዝግጅቱን በቅርቡ ለተመልካቾች ያደርሳል።
Arts tv

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...