የዶ/ር ደረጀ ዘለቀ ከዚህ ዓለም በሞት መለየት ሁለተኛ ዓመት መታሰቢያ ፕሮግራም እሁድ ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት አዳራሽ ተካሄዷል።
በፕሮግራሙ ላይ ቤተሰቦች፣ ጓደኞች፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስራ ባልደረቦች፣ ተማሪዎች፣ ጋዜጠኞች እና አርቲስቶች ተገኝተዋል።
በዝግጅቱ ላይ የክራር ጨዋታ፣ መነባንብ እና የዶ/ር ደረጄን አስተማሪነት፣ የህግ እውቀትና የምርምር ስራዎች የሚዘክሩ ልዩ ልዩ ዲስኩሮች ቀርበዋል።
እንዲሁም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኘው “ዶ/ር ደረጄ መታሰቢያ አፀደ ህፃናትና ቤተመጽሐፍ” ግብአት የሚሆኑ መጻሕፍት እና የመማሪያ ቁሳቁሶች ተሰብስበዋል።
አዘጋጆቹ መታሰቢያው ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ከዩኒቨርሲቲው የህግ ክፍል መምህራን እና ከተለያዩ አካላት ጋር በመተባበር በህግ ጥናትና ምርምር ለሚያደርጉ ተማሪዎች የገንዘብ እገዛና የውድድር ድጋፍ ለማድረግ ማቀዳቸውን ገልጸዋል።
(ይትባረክ ዋለልኝ)
