የትራኮማ መከላከያ የመድኃኒት በሰቆጣ እደላ እየተካሄደ ነው

Date:

የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የትራኮማ መከላከያ የመድሀኒት እደላ ዘመቻ ከሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 7 ቀን እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውቋል ።

ዘመቻው ማንኛውም በከተማ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን የሚያሳትፍ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዘመቻው ከ47ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተደራሽ እንደሚያደርግ ጤና ጽ/ቤቱ አስታውቋል።

ከዘመቻውም ጎን ለጎንም ማንኛውም ከ15 ዓመት በላይ የሆነ የከተማዋ ነዎሪዎች የዓይን ፀጉር መቀልበስ ልየታ እየተሰራ ሲሆን የዓይን ጸጉር መቀልበስ ችግር ያለባችሁ ህክምናው የሚሰጥ መሆኑን አውቀው ህክምናውን እንዲያገኙ ጽ/ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።

በተጨማሪም ለዘመቻው መሳካት የከተማው ማህበረሰብ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ሲል ጤና ተቋሙ መጠየቁን ብስራት ከሰቆጣ ከተማ ኮሙኒኬሽን ያገኘው መረጃ ያሳያል::

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...