የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከ59 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ገለጸ

Date:

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተሻለ የትምህርት ተቋም ለመሆን በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ 59 ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልገው የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝደንት ሳሙኤል ክፍሌ አስታወቁ።

ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በዓመት ከአራት ቢሊየን ብር የመንግስት በጀት እንዲሁም ከአንድ ቢሊየን ብር የራሱ ገቢ ያገኛል።

ሆኖም ፕሬዝደንቱ ይህ በቂ እንዳልሆነና ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራቱን ለማሻሻል፣ ምርምሮችን ለማስፋፋትና ለተማሪዎች ምቹ የሆነ የትምህርት ከባቢ ለመፍጠር በዓመት ከ11 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ተናግረዋል።

የገንዘብ እጥረት ዩኒቨርሲቲው እነዚህን ግቦች ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየሆነ መሆኑንም ፕሬዝደንት ሳሙኤል ክፍሌ ገልጸዋል።

ቅዳሜገበያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...