የአፍሪካ ዋንጫ በየአራት ዓመቱ እንደሚካሄድ ካፍ አስታወቀ

Date:

ከ2028 ጀምሮ የአፍሪካ ዋንጫ አሁን እየተካሄደበት ያለውን ፎርም በመቀየር በየአራት ዓመቱ እንደሚካሄድ የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞሴፔ አስታወቁ።

ይሄ ውሳኔ የተላለፈው ዛሬ በሞሮኮ ራባት በተደረገው የካፍ ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ ነው።

የአፍሪካ ዋንጫ ከ1968 ጀምሮ በየሁለት ዓመቱ ሲካሄድ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን፥በ2012 እና 2013 ብቻ በአንድ ዓመት ልዩነት ተካሂዷል።

የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ በሶስቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት (ኬንያ፣ ኡጋንዳ እና ታንዛኒያ) የጋራ አስተናጋጅነት ይካሄዳል።

ከቀጣዩ ዓመት (2028) አንስቶ ግን በየአራት ዓመቱ መካሄድ ይጀምራል።

ከ2029 አንስቶ ደግሞ ልክ እንደ አውሮፓው ሁሉ የአፍሪካ ኔሽንስ ሊግ ዋንጫ እንደሚጀመርና በየዓመቱ እንደሚካሄድም የካፍ ፕሬዝዳንት ሞሴፔ አስታውቀዋል።

ምስጋናው ታደሰ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...