የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የብድር ጣሪያን ማንሳቱን አስታወቀ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ከዚህ ቀደም በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን ጊዜያዊ የብድር ጣሪያ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን ገልጿል። ይህ ውሳኔ ወደ ገበያ መር የገንዘብ ፖሊሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰደ እርምጃ መሆኑ ተጠቅሷል።

የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ባንኩ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔን በአንድ በመቶ ከፍ አድርጓል። በተጨማሪም የዋጋ ግሽበትን ለመከላከል የሚያስችል አዲስ የታለመ የመጠባበቂያ ግዴታ ማዕቀፍ አስተዋውቋል።

ከውጭ ንግድ ጋር በተያያዘም ባንኩ የውጭ ምንዛሪ ኮሚሽንን ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ ዝቅ አድርጓል። እንዲሁም ላኪዎች የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሪ ለባንክ የመሸጥ ግዴታ (Surrender requirement) ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ በማድረግ፣ የላኪዎችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግና የውጭ ምንዛሪ ገበያውን ለማጠናከር አቅዷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከጂሃድና ከእምቢተኝነት ውጭ ሌላ መንገድ የለም!

የኢራኑ ከፍተኛ መሪ ሞጅተባ ኻመነኢ እሁድ ዕለት በቴሌግራም ገጻቸው...

አሜሪካ እና ኢራን ዳግም ወደ ድርድር ?

ኢራን ከአሜሪካ ጋር በሚደረገው ድርድር ሙሉ በሙሉ እንዳልወጣች፣ ነገር...

እስራኤል በጋዛ በፈፀመችው ጥቃት የሐማስ ከፍተኛ የደኅንነት ባለሥልጣን መገደሉ ተዘገበ

እስራኤል እሁድ ዕለት በጋዛ በፈፀመችው ጥቃት በሐማስ የሚመራው የፍልስጤም...

አሰቃቂውን ጥቃት የፈጸሙ ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ ፓትርያርኩ ጠየቁ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት...