የኢትዮጵያ ብር ከዓለማችን እጅግ ደካማ ገንዘቦች መካከል አንዱ ሆነ

Date:

እየተገባደደ በሚገኜው የውሮፓውያኑ 2025 ዓመት የኢትዮጵያ ብር ከዓለማችን እጅግ ደካማ ገንዘቦች መካከል አንዱ ሆኖ መመዝገቡ ተገለጸ።

በየጊዜው እያሽቆለቆለ ለመጣው የኢትዮጵያ ብር መዳከም በርካታ መንስኤዎች ቢኖሩም ዋነኛው ግን የኢኮኖሚው አለመረጋጋት መሆኑንም “ኤክስኤስ.ኮም” የተባለ የምጣኔ ሀብት ተቋም ከሰሞኑ ይፋ ያደረገው መረጃ አመላክቷል።

በተቋሙ መረጃ መሠረት በዓመቱ ከዓለማችን እጅግ ደካማ ገንዘብ ካላቸው ሀገራት መካከል ኢራን ሊባኖስን እና ዚምባብዌን አስከትላ የአንደኝነቱን ደረጃ የያዘች ሲሆን ኢትዮዸያ ደግሞ ከየመን ቀጥሎ ከሀይቲ ደግሞ ተሽላ በ26ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።

የኢትዮጵያ ብር ባለፈው የጎርጎሪዮሱ ዓመትም ከሰሐራ በታች ካሉ ደካማ ገንዘብ ካላቸው አገራት ተርታ እንደሚመደብ የዓለም ባንክ ባወጣው መረጃ መግለጹ ይታወሳል።

መንግሥት ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት እና ከብር መዳከም ጋር ተያያዘ የሚከሰተውን የዋጋ ግሽበት ለመቀነስ የተለያዩ ፖሊሲዎችን እና መመሪያዎችን እየተገበረ መሆኑን በተደጋጋሚ ሲገልጽ ይሰማል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን በመከተል የዋጋ ግሽበቱን ለማርገብና ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት የሚያስችሉ ውሳኔዎችን ማሳለፉን በቅርቡ አራተኛ ጉባኤውን ባከናወነበት ወቅት መግለቱም አይዘነጋም።

(#አዲስ_ማለዳ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...