የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የኢ ሰርቪስ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር አስታወቀ

Date:

የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የንግድ ምልክትና የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምዝገባ አገልግሎቶችን ለማዘመን የኤሌክትሮኒክ (e -service) አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነት እና ኮምኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ ለብስራት ሬዲዮ ጨምረው ገልፀዋል።

የተገልጋይ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የገለፁት አቶ ኤልያስ የአገልግሎት ተደራሽነቱን ለማስፋት እና ዘመኑን ያማከለ አሰራር ለመዘርጋት የኤሌክትሮኒክስ አገልግሎት መጀመሩ በእጅጉ ያግዛል ብለዋል።በተለይም ሃገሪቷ የጀመረችውን የዲጅታል ኢኮኖሚ እውን ለማድረግ እንደተቋም የሚያበረክተው ሚና እንዳለ ገልፀዋል ።

የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ያለውን ሰፊ አገልግሎቶች ዘመናዊ ለማድረግና ተገልጋዮቹን የበለጠ ለማርካት አለም አሁን ያለችበትን የዲጅታል ዘመን ባማከለ መንገድ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስፈልግ ገልፀው ተጨማሪ ስልጠናዎች እንዲሁም ሌሎች የድጋፍ ስራዎችም መስራት እንደሚያስፈልግም አቶ ኤሊያስ መሀመድ ተናግረዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...