የኢትዮጵያ የቋንቋ ሀብት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተዘከረ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባህልና ኪነ-ጥበብ ቢሮ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትብብር የተዘጋጀው ልዩ የውይይት መድረክ፣ “የወጣቶች ተሳትፎ በልሳነ-ብዙ የትምህርት ስርዓት ለኢትዮጵያ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል በአንጋፋው ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ26ኛ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ3ኛ ጊዜ የተከበረው ይህ ዕለት፤ ኢትዮጵያ የበርካታ ቋንቋዎችና ባህሎች ባለቤት መሆኗን በማጉላት፣ ለዘርፉ ዘላቂ ዕድገት ከምሁራን ጋር በጋራ ለመስራትና ጠንካራ የፖሊሲ ድጋፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ ላይ የምልክት ቋንቋን በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ማካተትን ጨምሮ የኢትዮጵያ የቋንቋ ሥርዓተ-ትምህርት ታሪካዊ ጉዞ ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የባህል ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ አዲሱ ሻንቆ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ቋንቋ ባህልና እሴቶቻችንን የምንገልጽበት ትልቅ ሀብትና ውበታችንን የምናሳይበት ድልድይ መሆኑን ገልጸው፣ መንግስት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።

መድረኩ በልሳነ-ብዙ ትምህርት ዙሪያ ያሉ ተግዳሮቶችን በመለየትና ለወደፊት የሥራ አቅጣጫዎች ጠቋሚ የሆኑ ሃሳቦችን በማንሳት በስኬት ተጠናቋል። ይህ መሰል መድረክ የሀገራችንን ብዝሃነት እንደ አንድ ትልቅ አቅም በመጠቀም ለጋራ ብልጽግና የምናደርገውን ጉዞ የሚያፋጥን መሆኑ ተመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ቴዲ አፍሮ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ቀይሮታል!” — ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

በ"ወቸው ጉድ" ፖድካስት ላይ እንግዳ ሆነው የቀረቡት ፕሮፌሰር ብርሃኑ...

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...