አምዞን እና ዴልታ አየር መንገድ የሳተላይት ኢንተርኔት ስምምነት ተፈራረሙ

Date:

የአማዞን ኩባንያ የሳተላይት ኢንተርኔት ክፍል  ከዴልታ አየር መንገድ ጋር በ500 አውሮፕላኖች ላይ የዋይ ፋይ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ስምምነት መፈራረሙን አስታውቋል።

እ.ኤ.አ. በ2028 አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ስምምነት፣ አማዞን በዘርፉ ቀዳሚ ከሆነው የኢሎን ማስክ ‘ስታርሊንክ’ ጋር ያለውን ፉክክር ይበልጥ እንደሚያፋጥነው ተነግሯል።

ስታርሊንክ በአሁኑ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ ሳተላይቶችን ወደ ህዋ በማምጠቅ የገበያ የበላይነቱን ቢይዝም፣ አማዞን ግን ከዴልታ በፊት ከጄት ብሉ ጋር በደረሰው ስምምነት መሰረት የገበያ ድርሻውን ለማስፋት በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

ኩባንያው ከኤፕሪል 2025 ጀምሮ 214 ሳተላይቶችን ወደ ህዋ ያመጠቀ ሲሆን፣ በሚቀጥሉት 12 ወራት ውስጥ ከ20 በላይ መንኮራኩሮችን በመጠቀም የማምጠቅ አቅሙን እጥፍ ለማድረግ አቅዷል።

ዴልታ አየር መንገድ አማዞንን ለዚህ አገልግሎት የመረጠውም ቀደም ሲል ከአማዞን ዌብ ሰርቪስ ጋር ባለው ጠንካራ የክላዉድ ስሌት ሥራ ትብብር ምክንያት እንደሆነ ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

መርስክ የበርበራ ወደብ የጭነት አገልግሎቶችን ለጊዜው አቋረጠ

የዓለማችን ግዙፍ የመርከብ ድርጅት የሆነው መርስክ ፣ ወደ በርበራ...

የምርጫ ካርድ፡ የአገር ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ

ግዮን መጽሔት :- በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዞ ውስጥ ምርጫዎች የሥልጣን...

አደይ ኢትዮጵያ ጓል አስመራ…!!

የቀድሞ ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የስንብት ቃል ለጠቅላይ ሚ/ር ዐብይ...

ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ሁለተኛው ዙር ድርድር ሊደረግ እንደሚችል ተናገሩ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ሁለተኛ ዙር የሰላም ድርድር...