የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኦስማን ሳለህ፣ ኢትዮጵያ የተሳሳተና ጊዜው ያለፈበት በኃይል ወይም በዲፕሎማሲዊ መንገድ የባሕር ኃይል የማቋቋም ወይም የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ ኤርትራን እያስገረማት እንደኾነ ለዲፕሎማቶች በሠጡት ማብራሪያ ተናግረዋል።
ኦስማን፣ ኢትዮጵያ የጎረቤቶቿን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት እንድታከብር ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ግፊት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
የኤርትራ ጦር ኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛል የሚሉ አካላት፣ ለኢትዮጵያ ውስጣዊ ችግር ኤርትራን ተጠያቂ ማድረግ የሚፈልጉ ናቸው በማለትም ኦስማን ከሰዋል።
ኦስማን፣ በሕወሓትና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል ባለው ሽኩቻ ውስጥ ኤርትራ ሚና አላት የሚለውን ውንጀላም አስተባብለዋል።
Via ዋዜማ
