የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የጎረቤቶቿን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት እንድታከብር ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ግፊት እንዲያደርግ ጠየቁ

Date:

የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኦስማን ሳለህ፣ ኢትዮጵያ የተሳሳተና ጊዜው ያለፈበት በኃይል ወይም በዲፕሎማሲዊ መንገድ የባሕር ኃይል የማቋቋም ወይም የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ ኤርትራን እያስገረማት እንደኾነ ለዲፕሎማቶች በሠጡት ማብራሪያ ተናግረዋል።

ኦስማን፣ ኢትዮጵያ የጎረቤቶቿን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት እንድታከብር ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ግፊት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

የኤርትራ ጦር ኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛል የሚሉ አካላት፣ ለኢትዮጵያ ውስጣዊ ችግር ኤርትራን ተጠያቂ ማድረግ የሚፈልጉ ናቸው በማለትም ኦስማን ከሰዋል።

ኦስማን፣ በሕወሓትና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል ባለው ሽኩቻ ውስጥ ኤርትራ ሚና አላት የሚለውን ውንጀላም አስተባብለዋል።

Via ዋዜማ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...