የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የጎረቤቶቿን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት እንድታከብር ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ግፊት እንዲያደርግ ጠየቁ

Date:

የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኦስማን ሳለህ፣ ኢትዮጵያ የተሳሳተና ጊዜው ያለፈበት በኃይል ወይም በዲፕሎማሲዊ መንገድ የባሕር ኃይል የማቋቋም ወይም የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ ኤርትራን እያስገረማት እንደኾነ ለዲፕሎማቶች በሠጡት ማብራሪያ ተናግረዋል።

ኦስማን፣ ኢትዮጵያ የጎረቤቶቿን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት እንድታከብር ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ግፊት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

የኤርትራ ጦር ኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛል የሚሉ አካላት፣ ለኢትዮጵያ ውስጣዊ ችግር ኤርትራን ተጠያቂ ማድረግ የሚፈልጉ ናቸው በማለትም ኦስማን ከሰዋል።

ኦስማን፣ በሕወሓትና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል ባለው ሽኩቻ ውስጥ ኤርትራ ሚና አላት የሚለውን ውንጀላም አስተባብለዋል።

Via ዋዜማ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...