የዋሊያ አይቤክስን ደህንነት ለመታደግ ያለመ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ይፋ ተደረገ፡፡ ዕቅዱ ይፋ የሆነው የዋሊያ አይቤክስን ቁጥርን ለመመለስና ለማሣደግ ያለመ ውይይት በጎንደር ከተማ በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡
በሺዎች ይቆጠር የነበረው ዋልያ አይቤክስ ወደ 300 ዝቅ ማለቱን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በቅርቡ ማስታወቁ ይታወሳል።
ስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ኃላፊነት ያለባቸው አካላት ተቀናጅተው በመሥራት የሀገር ምልክት የሆነውን ዋሊያ አይቤክስ ከተጋረጠበት አደጋ እንዲከላከሉ የሚያስችላቸው ነው ተብሏል።
