“የዓድዋ ፓን አፍሪካን ዩኒቨርሲቲ” ምስረታ እንደሚበሰር ተገለጸ

Date:



የዓድዋ ድልን ታሪካዊ ፋይዳ ለትውልድ ለማስተላለፍና የአፍሪካውያንን አንድነት ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችል “የዓድዋ ፓን አፍሪካን ዩኒቨርሲቲ” ለመመሥረት ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሆነ እና በ130ኛው በዓል ለዓለም ይፋ እንደሚደረግ የተናገሩት ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ ናቸው።

በ130ኛው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ይፋ እንደሚደረግ የሚጠበቀው የተቋሙ ወደ ሥራ መግባት ዝርዝር መግለጫዎች እየተዘጋጁለት እንደሆነ ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።

ይህ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ከታሪክ ዘካሪነቱ ባለፈ፣ የፓን አፍሪካኒዝም መንፈስን በተደራጀ የዕውቀት ዘርፍ ለማሳደግ ያለመ እንደሆነም ተነግሯል።

ላለፉት 56 ዓመታት የዓድዋን ድል በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲያስተዋውቁ የቆዩት ፕሮፌሰር ማሞ፣ ድሉ በተለይም እሳቸው ሚያስተምሩበት የደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ያሉ እና ከዓለም ዙሪያ የተሰባሰቡ

አፍሪካውያን ምሁራን በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ ላለፉት 11 ዓመታት በድምቀት ሲከበር እንደነበር አስታውሰዋል።
ድሉ በኬፕ ታውን እንዲከበር የተደረገበት ዋና ምክንያትም ነጮች ስለ ድሉ ጥልቀት እንዲረዱ፣ ጥቁሮች ደግሞ ከታሪካዊ ድላቸው እንዲማሩ እንደሆነ ምሁሩ አብራርተዋል።

በኬፕታውን ከተማ በሚካሄደው የምሁራኑ የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ላይ ከተገኙ ታላላቅ ሰዎች መካከል የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ታቦ እምቤኪ እንደሚገኙበት ያስታወሱት ፕሮፌሰር ማሞ፣ 130ኛው የዩኒቨርሲቲው ምሥረታ ይፋ የሚደረግበት እንዲሆን እየተሠራ እንደሆነ ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲውን ለመገንባት የሚያስፈልገውን የገንዘብ ምንጭ በተመለከተ፣ በራስ አቅም የመቆም ጽኑ አቋም ቢኖርም የድሉን ትርጉም የሚረዱ በርካታ አገራት ፕሮጀክቱን ለመደገፍ ፍላጎት ማሳየታቸውና ንግግር እየተደረገባቸው መሆኑ ታውቋል።

በአጠቃላይ “የዓድዋ ፓን አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ” የምሥረታ እንቅስቃሴ፣ የዓድዋን ድል ከወታደራዊ ድልነት ወደ አህጉራዊ የልህቀትና የዕውቀት ተቋምነት ለማሸጋገር የሚደረግ ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ ነው ተብሏል።

(አሐዱ ራድዮ) 

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ቴዲ አፍሮ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ቀይሮታል!” — ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

በ"ወቸው ጉድ" ፖድካስት ላይ እንግዳ ሆነው የቀረቡት ፕሮፌሰር ብርሃኑ...

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...