የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

Date:

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሁለተኛውን የጣሊያን-አፍሪካ ጉባዔ በጋራ በምናስተናግድበት በዚህ ወቅት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒን ወደ ኢትዮጵያ እንኳን ደህና መጡ ስል ታላቅ ደስታ ይሰማኛል ብለዋል።

‎አጋጣሚው ዲፕሎማሲያዊ ስብሰባ ብቻ እንዳልሆነ ገልጸው፤ በጣሊያንና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው ጠንካራ አጋርነት ማሳያ እንደሆነ አንስተዋል።

ይህም አጋርነት በመከባበር፤ በጋራ ኃላፊነትና ለዘላቂ ዕድገት ባለን የጋራ ርዕይ ላይ የተመሠረተ ነው ብለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ሜሎኒ ጉብኝት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በኢነርጂ፣ በመሠረተ ልማት፣ በግብርና እና በፈጠራ ዘርፎች የቀጠለውን ትብብራችን ለማጠናከር ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ ነው ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የዓለም የቡና ገበያ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ተገለጠ

በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና አቅርቦት ላይ ተፈጥሮ የነበረው ስጋት...

አሜሪካ የኢራንን የጭነት መርከብን መያዟን አስታወቀች

በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን የዘጋችው...

“ቴዲ አፍሮ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ቀይሮታል!” — ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

በ"ወቸው ጉድ" ፖድካስት ላይ እንግዳ ሆነው የቀረቡት ፕሮፌሰር ብርሃኑ...