የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

Date:

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሁለተኛውን የጣሊያን-አፍሪካ ጉባዔ በጋራ በምናስተናግድበት በዚህ ወቅት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒን ወደ ኢትዮጵያ እንኳን ደህና መጡ ስል ታላቅ ደስታ ይሰማኛል ብለዋል።

‎አጋጣሚው ዲፕሎማሲያዊ ስብሰባ ብቻ እንዳልሆነ ገልጸው፤ በጣሊያንና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው ጠንካራ አጋርነት ማሳያ እንደሆነ አንስተዋል።

ይህም አጋርነት በመከባበር፤ በጋራ ኃላፊነትና ለዘላቂ ዕድገት ባለን የጋራ ርዕይ ላይ የተመሠረተ ነው ብለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ሜሎኒ ጉብኝት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በኢነርጂ፣ በመሠረተ ልማት፣ በግብርና እና በፈጠራ ዘርፎች የቀጠለውን ትብብራችን ለማጠናከር ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ ነው ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...