የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠንካራ ተፎካካሪነታቸው መዳከሙ ተገለፀ

Date:

የፖለቲካ ፓርቲዎች ከጠንካራ ተፎካካሪነት ይልቅ ወደ ግልና ቡድን ግንባታ ዝቅ ብለዋል ሲል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግሯል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ፀሐፊ አቶ ደስታ ዲንቃ ከጣቢያችን ጋር በነበራቸው ቆይታ “በኢህአዴግ ጊዜ ቢያንስ ጠንካራ ተፎካካሪ የሚባሉና ኢህአዴግ ራሱ የሚፈራቸው ፓርቲዎች ነበሩ፤ ስልጣን ባይሰጣቸው እንኳ የሚያነሱትን ሃሳብ ተግባራዊ ለማድረግ ይሯሯጥ ነበር” ያሉ ሲሆን “በአሁኑ ጊዜ ግን የፖለቲካ ፓርቲዎችም የፖለቲካ መሪዎች የሚባሉትም አሁን ራሳቸውንና ቡድናቸውን ወደ መገንባት፣ ወደ ግልና ቡድን ጥቅም ዝቅ ያሉበት ሁኔታ ነው የማስተውለው” በማለት ተናግረዋል።

በፖለቲካ ፓርቲዎች ዘንድ በትብብር ላይ የተመሰረተ ፉክክር ለማድረግ ራሳቸውን አዘጋጅተው ፖለቲካን የመስራት ሁኔታ እንደማይስተዋል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ፀሐፊው ገልፀዋል። የፖለቲካ ምህዳሩ መስፋት አለበት በሚለው ላይ ሁሉም ቢስማሙም፣ ነገር ግን ‘ባይሰፋም ችግር የለም’ የሚሉ የመንግስትን ስራ ብቻ የሚደግፉ አሉ በተጨማሪም ምህዳሩ ቢሰፋም፣ ባለበት ቢቀጥልም ችግር የሌለባቸው የፖለቲካ ፓርቲዎችም አሉ በማለት አቶ ደስታ ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።

በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል እምብዛም በመርህ ላይ የተመሰረተ ትብብርና ግንኙነት እንደማይስተዋል ገልፀው፣ የተከፋፈለና አንዱ ሌላውን የማዳመጥ ባህል ያልዳበረ ስለሆነ ቤታቸውን ዘግተው ነው የተቀመጡት ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

መረጃ በማይሰጡ ኃላፊዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ የሚያስችል ሕግ ተዘጋጀ

የመገናኛ ብዙሃን እና የመረጃ ነፃነት የየራሳቸው ባህሪ ቢኖራቸውም እስካሁን...

የ30 ዓመታትን ጉዞ የሚዘክረው ዳሸን ኤክስፖ

የዳሸን ባንክን 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀው...

‹‹ሀገር ጥለው የጠፉና ድርጅቶቻቸውን ለመዝጋት የተገደዱ አሉ››

አቶ አለማየሁ ከተማ(የኢትዮጵያ ሪልስቴት አልሚዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት) ግዮን መጽሔት :-...

የሰላም ስምምነት ሳይፈጸም የንግድ መርከቦች ጉዞ እንደማይጀምሩ የነዳጅ ጫኝ ኩባንያ ኃላፊ ተናገሩ

የሲውዲን ነዳጅ አጓጓዥ ኩባንያ የሆነው ‘ስቴና በልክ’ ዋና ስራ...