የታሪካዊው ቁልቢ ገብርኤል የዕድሳት ጥሪ ፦ የ134 ሚሊዮን ብር ግዙፍ ፕሮጀክት

Date:

!

ከተገነባ 64 ዓመታትን ያስቆጠረውና በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ምዕመናን የሚሳለሙት የታሪካዊው የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን፣ በአሁኑ ወቅት ሰፊ የዕድሳት ሥራ እየተከናወነለት ይገኛል።

ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት በተሰጠ መግለጫ፣ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስና ሌሎች ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት የሕንጻውን ጥንታዊ ይዘት ለመጠበቅና የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የጥገና ሥራ መጀመሩ ይፋ ሆኗል።

የዕድሳቱ ዋና ዓላማ በጊዜ ብዛትና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በቤተክርስቲያኑ ጣሪያና ግድግዳ ላይ የደረሱ ጉዳቶችን በባለሙያዎች የታገዘ ጥገና በማድረግ የታሪካዊ ቅርሱን ዕድሜ ማራዘም ነው።

ፕሮጀክቱ የመቅደሱን፣ የቅኔ ማሕሌቱንና የአጸዱን የማዘመን ሥራዎችን የሚያካትት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ግንባታው በሁለት ፈረቃ ተከፍሎ በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተከናወነ 40 በመቶ ያህሉ መጠናቀቁ ተገልጿል።

ለዚህ ግዙፍ የዕድሳት ሥራ ከ134 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚያስፈልግ የተጠቆመ ሲሆን፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚገኙ ምዕመናን በገዳሙ ስም በተከፈቱ የባንክ ሒሳቦች አማካኝነት በገንዘብ፣ በጸሎትና በጉልበት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

‹‹ሀገር ጥለው የጠፉና ድርጅቶቻቸውን ለመዝጋት የተገደዱ አሉ››

አቶ አለማየሁ ከተማ(የኢትዮጵያ ሪልስቴት አልሚዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት) ግዮን መጽሔት :-...

የሰላም ስምምነት ሳይፈጸም የንግድ መርከቦች ጉዞ እንደማይጀምሩ የነዳጅ ጫኝ ኩባንያ ኃላፊ ተናገሩ

የሲውዲን ነዳጅ አጓጓዥ ኩባንያ የሆነው ‘ስቴና በልክ’ ዋና ስራ...

መርስክ የበርበራ ወደብ የጭነት አገልግሎቶችን ለጊዜው አቋረጠ

የዓለማችን ግዙፍ የመርከብ ድርጅት የሆነው መርስክ ፣ ወደ በርበራ...

የምርጫ ካርድ፡ የአገር ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ

ግዮን መጽሔት :- በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዞ ውስጥ ምርጫዎች የሥልጣን...