ደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ዓለም የሚፈልጋቸው ማዕድናት ያሉበት አካባቢ ነው

Date:

በደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ያሉ አካባቢዎች አሁን ዓለም የሚፈልጋቸው ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት አካባቢ መሆኑን የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኢንዱስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማዕድን ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል፡፡

የማዕድን  ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ እንደገለጹት፤ በደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ያሉ አካባቢዎች አሁን ዓለም የሚፈልጋቸው ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት አካባቢ ነው፡፡

የአገሪቱ አንደኛ ደረጃ የሚባሉ ማዕድናትን ፍለጋ ላይ እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በጉጂ፣ ቦረና፣ ከፊል ሶማሌ፣ ሱማሊያና ኬንያ ድንበር እና ሰቆጣ አካባቢ ያለው የብረት ክምችት ጥናት እየተካሄደ ነው ብለዋል፡፡

እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ አካባቢዎቹ ሊቲየም፣ ታንታለም፣ ኒኬል፣ ማንጋኒዝ የሚባሉ ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት ነው፡፡

በውስን አቅም ቢሆንም በእነዚህ አካባቢዎች ላይ የምርመራ ሥራዎች እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ የአገር ፍላጎትን መሰረት በማድረግ በቅደም ተከተል በመሰራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ጋዜጣ ፕላስ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...