ደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ዓለም የሚፈልጋቸው ማዕድናት ያሉበት አካባቢ ነው

Date:

በደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ያሉ አካባቢዎች አሁን ዓለም የሚፈልጋቸው ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት አካባቢ መሆኑን የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኢንዱስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማዕድን ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል፡፡

የማዕድን  ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ እንደገለጹት፤ በደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ያሉ አካባቢዎች አሁን ዓለም የሚፈልጋቸው ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት አካባቢ ነው፡፡

የአገሪቱ አንደኛ ደረጃ የሚባሉ ማዕድናትን ፍለጋ ላይ እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በጉጂ፣ ቦረና፣ ከፊል ሶማሌ፣ ሱማሊያና ኬንያ ድንበር እና ሰቆጣ አካባቢ ያለው የብረት ክምችት ጥናት እየተካሄደ ነው ብለዋል፡፡

እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ አካባቢዎቹ ሊቲየም፣ ታንታለም፣ ኒኬል፣ ማንጋኒዝ የሚባሉ ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት ነው፡፡

በውስን አቅም ቢሆንም በእነዚህ አካባቢዎች ላይ የምርመራ ሥራዎች እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ የአገር ፍላጎትን መሰረት በማድረግ በቅደም ተከተል በመሰራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ጋዜጣ ፕላስ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...