በትግራይ ክልል 1.2 ሚሊየን ልጆች ወደ ትምህርት ገበታ አልተመለሱም

Date:

በትግራይ ክልል 1.2 ሚልዮን ሕፃናት እና አዳጊ ልጆች ወደ ትምህርት ገበታ አለመመለሳቸው ተገለጸ።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንደገለጸው በትግራይ ከጦርነቱ በኋላ ጭምር የቀጠለው ሰብአዊ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግር ሚልዮኖች ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ አድርጓል።

በዚህም ላይ እስካሁን መፍትሔ ያላገኘው የተፈናቃዮች ጉዳይ ሌላው ልጆች ትምህርት ቤት እንዳይ ሄዱ እንቅፋት እንደሆነም ተገልጿል።

በዚህ ዓመት በትግራይ ክልል 2.5 ሚልዮን ተማሪዎች ነበሩ ወደ ትምህርት ቤት ይገባሉ ተብሎ የታሰበው፤ ሆኖም አሁን በትምህርት ገበታ ላይ የሚገኙት 1.3 ሚልዮን ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሐላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዑሽ ተናግረዋል።

ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ ተማሪዎች ቁጥር ከመቀነሱ ጎን ለጎን የትምህርት ጥራቱ ላይም ክፍተት እየተስተዋለ መሆኑ ተነግሯል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...