በትግራይ ክልል 1.2 ሚሊየን ልጆች ወደ ትምህርት ገበታ አልተመለሱም

Date:

በትግራይ ክልል 1.2 ሚልዮን ሕፃናት እና አዳጊ ልጆች ወደ ትምህርት ገበታ አለመመለሳቸው ተገለጸ።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንደገለጸው በትግራይ ከጦርነቱ በኋላ ጭምር የቀጠለው ሰብአዊ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግር ሚልዮኖች ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ አድርጓል።

በዚህም ላይ እስካሁን መፍትሔ ያላገኘው የተፈናቃዮች ጉዳይ ሌላው ልጆች ትምህርት ቤት እንዳይ ሄዱ እንቅፋት እንደሆነም ተገልጿል።

በዚህ ዓመት በትግራይ ክልል 2.5 ሚልዮን ተማሪዎች ነበሩ ወደ ትምህርት ቤት ይገባሉ ተብሎ የታሰበው፤ ሆኖም አሁን በትምህርት ገበታ ላይ የሚገኙት 1.3 ሚልዮን ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሐላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዑሽ ተናግረዋል።

ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ ተማሪዎች ቁጥር ከመቀነሱ ጎን ለጎን የትምህርት ጥራቱ ላይም ክፍተት እየተስተዋለ መሆኑ ተነግሯል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...