የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን እንዳስታወቀው የገቢዎች ሚኒስቴርና ጉምሩክ ኮሚሽን ከታክስና ቀረጥ ጋር በተያያዘ ነጋዴዎች ያቀረቡትን ይግባኝ ተከትሎ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የሰጡትን ውሳኔ በወቅቱ ለመፈጸም ፈቃደኛ አለመሆናቸው ከፍተኛ ቅሬታ አስከትሏል።
ኮሚሽኑ ይህን ቅሬታ የገለጸው በግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም. የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸምና ከ2011 እስከ 2017 ዓ.ም. ያለውን የስድስት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም በሚመለከት በሰጠው መግለጫ ነው።
የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉጌታ አያሌው እንደገለጹት፣ በኮሚሽኑ ውሳኔዎች ቅር የተሰኙ ግብርና ቀረጥ ከፋይ ነጋዴዎች ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ይጠይቃሉ ሲል የዘገበው ሪፖርተር ነዉ።
