ግብር መክፈያ ጊዜ የሂሳብ ሪፖርት አቀራረብ ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት

Date:

የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የቅድሚያ ግብር ክፍያ ጊዜን አስመልክቶ አዲስ ማብራሪያ ሰጥቷል። ሚኒስቴሩ እንዳስታወቀው፣ የቅድሚያ ግብር የሚከፈለው በየሦስት ወሩ ሲሆን፣ የጊዜው ስሌት የሚጀምረው የሂሳብ ሪፖርት ከቀረበበት ወር ማብቂያ ጀምሮ ነው።

​ሚኒስትሩ ለገቢዎች ቢሮ የፃፈዉ ደብዳቤ ላይ ግብር ከፋዮች የየሦስት ወሩን የቅድሚያ ግብር ክፍያ፣ የሂሳብ ሪፖርት ካቀረቡበት ወር በኋላ ባሉት በየሦስት ወሩ መጨረሻ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ መፈጸም ይጠበቅባቸዋል።

​በዚህ ማብራሪያዉ ላይ እንደጠቆመዉ የሂሳብ ሪፖርታቸውን በጥቅምት ወር የሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች፣ የመጀመሪያውን ቅድሚያ ግብር በየካቲት ወር፣ ሁለተኛውን በግንቦት ወር፣ ሦስተኛውን ደግሞ በነሐሴ ወር ይከፍላሉ። በተጨማሪም፣ ዓመታዊ ግብራቸውን አጠቃለው እስከ ጥቅምት ወር መጨረሻ ድረስ መክፈል እንደሚኖርባቸው በዝርዝር አስቀምጧል።

ይህን ተከትሎ ​ የሂሳብ ሪፖርት የሚቀርብበት ወር የግብር ክፍያ ማጠናቀቂያ ወር እንደሚሆን የገለፀ ሲሆን በዚህም መሰረት፣ አንድ ግብር ከፋይ በየሦስት ወሩ የከፈለው ቅድሚያ ግብር ከጠቅላላ ዓመታዊ ግብሩ ያነሰ ከሆነ፣ የቀረውን ልዩነት መክፈል ግዴታ እንዳለበት አፅንኦት ሰጥቷል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...