ግብፅ 40,000 ወታደሮችን ወደ ሲና ድንበር አሰማራች

Date:

ግብፅ በ1979 ከእስራኤል ጋር ባደረገችው የሰላም ስምምነት መሠረት ከተፈቀደው ቁጥር በእጥፍ የሚጠጋ 40,000 ወታደሮችን ወደ ሰሜን ሲና አሰማርታለች።

ግብፅ ወታደሮቿን ያሰማራችው እስራኤል በጋዛ የምታደርገው ወታደራዊ ዘመቻ ፍልስጤማውያንን ወደ ግብፅ ግዛት ማፈናቀልን ሊፈጥር ይችላል በሚል ስጋት ነው።

ወደ ሲና ያቀናው የግብፅ ጦር የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን፣ የአየር መከላከያ ዘዴዎችን እና ልዩ ሃይሎችን ያካተተ ሲሆን በ ራፋህ እና ሼክ ዙዋይድ ባሉ ስትራቴጂካዊ ቦታዎች ላይ ሰፍረዋል።

እስራኤል ግብፅ ወታደሮቿን በማስጠጋቷ ደስተኛ እንዳልሆነች የገለፀች ቢሆንም ግብጽ እራሴን ለመከላከል ያደረኩት እርምጃ ነው ብላለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...