የአውሮፓ ህብረት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት የጋዛን ግጭት ለማስቆም ያሳለፈውን ውሳኔ እንደተቀበለው አስታወቀ ።
የጋዛን ግጭት እስከወዲያኛው ይፈታል ተብሎ የታመነበትን ባለ20 ነጥብ የሰላም ዕቅድ ለቀጣናው አጠቃላይ ገፅታ አስፈላጊ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል ።
የአውሮፓ ህብረት ቃል አቀባይ አኑዋር ኤል አኖኒ በብራሰልስ በሰጡት መግለጫ ፣ የተመድ ውሳኔ ሰብዓዊ እርዳታ በሚገባበት ፣የመልሶ ግንባታ በሚካሄድበት እና ተቋማዊ እድሳት በሚከናወንበት ሁኔታ መምከሩ እና ውሳኔ ላይ መድረሱ ትልቅ እርምጃ ነው ሲሉ አወድሰውታል ።
ህብረቱ ከተመድ እና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በመሆን በጋዛ አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ይሰራል ብለዋል ቃል አቀባዩ ።
ምን እንኳ የፀጥታው ምክር ቤት በጋዛ የሰላም እና ደህንነት አስከባሪ ሀይሎች እንደሚገቡ ከውሳኔ ቢደርስም ሀማስ ግን ውሳኔውን አልተቀበለውም ተብሏል ።
ሚድል ኢስት ሞኒተር እንደዘገበው ።
