ተወዳጆቹ አርቲስቶች ኮሜዲያን ደረጀ ሀይሌ እና ተዋናይ መኮንን ላዕከ በጃፓን ዋና ከተማ ቶኪዮ ለሚኖሩ ትዉልደ ኢትዮጵያዊያን የጥበብ ስራዎቻቸውን ለማቅረብ ጃፓን ቶኪዮ ገብተዋል።
ሁለቱ አርቲስቶች የፊታችን እሁድ September 7 / 2025 ዓ ም በቶኪዮ ካቱሺካ ሂጋሺታቲሺ ሴንተር ዉስጥ በሙዚቃ የታጀበ ልዩ የኮሜዲ ምሽት ያቀርባሉ። በዚህ ደማቅ የኮሜዲ ምሽት ላይ መታደም የመግቢያ ዋጋዉ 3000 የጃፓን የን ሲሆን የመግቢያ ትኬቱም በሊትል ኢትዮጵያ በመሸጥ ላይ ነው።
©️ይትባረክ ዋለልኝ
