ሄኖክ አርጋው ፋውንዴሽን፤ ከ50 ሚ. ብር በላይ የሚገመቱ የህክምና መሳሪያዎችን አበረከተ

Date:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ አሜሪካ የሚገኘው ሄኖክ አርጋው ፋውንዴሽን፣ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ 133 አይነት የተለያዩ የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችንና የህክምና ግብአቶችን ማበርከቱን ገልጸዋል፡፡

መሳሪያዎቹ ለኩላሊት፣ ለተኝቶ ታካሚዎች፣ ለፅኑ እና መደበኛ ሕሙማን ህክምና ግልጋሎት የሚያግዙ ናቸው።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልእክት፤ “ቸር ልብ ያላቸው እልፍ ዜጎች አሉን ፤ ከዲያስፖራ እስከ ሀገር ቤት ካላቸው የሚያካፍሉ፣ ከጎዶሎአቸው የሚሰጡ ፣ በመስጠት ውስጥ ያለን በረከት የተረዱ ፣ ለሀገሬ ምን አደረኩላት የሚሉ፣ ቸር፣ ሀብታም ልብ ያላቸዉ እልፍ ወንድም እህቶች አሉን።

ዛሬም በሀገረ አሜሪካ ኮሎራዶ ግዛት የሚገኘው “ሄኖክ አርጋው ፋውንዴሽን” ዋጋቸው ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ 133 አይነት የተለያዩ የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችንና የህክምና ግብአቶችን አበርክቶልናል” ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ሄኖክ አርጋው ፋውንዴሽንን በከተማ አስተዳደሩ፣ በተጠቃሚው ማህበረሰብና በራሴ ስም እጅግ አድርጌ እያመሰገንኩ፤ ድጋፉ ለታለመለት ዓላማ እንዲውልም ለአስተዳደሩ የጤና ቢሮ አስረክበናል ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...