ለእስራኤል ጦር ወግነው የሚዋጉ የብሪታኒያ ዜጎች በጋዛ የጦር ወንጀሎች ይጠይቃሉ ተባለ

Date:

በዩናይትድ ኪንግደም የሚገኘው የህግ ባለሙያዎች ቡድን ለእስራኤል ወግነው በጋዛ ጦርነት ላይ በተሳተፉ 10 የእንግሊዝ ዜጎች ላይ የጦር ወንጀል ክስ ለማቅረብ ማቀዱን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል። ቅሬታው ብሪታንያውያንን “በሲቪል አካባቢዎች ላይ ያለ አድሎአዊ ጥቃቶች” እና “በተከለከሉ ቦታዎች ላይ ታሪካዊ ሀውልቶችን እና ሃይማኖታዊ ቦታዎችን ጨምሮ በተጠበቁ ቦታዎች ላይ የተቀናጁ ጥቃቶች” ጋር እጃቸው አለበት ሲል ክስ መመስረቱን ይፋ አድርጓል።

በጉዳዩ ላይ ከተሳተፉት ጠበቆች መካከል አንዱ የሆኑት ታዋቂው ጠበቃ ሚካኤል ማንስፊልድ “የብሪታንያ ዜጎች በፍልስጤም ውስጥ ከተፈጸሙ ወንጀሎች ጋር እንዳይተባበሩ ህጋዊ ግዴታ አለባቸው፤ ማንም ከህግ በላይ አይደለም” ብለዋል። ማንስፊልድ የጠቀሰው የዘ ጋርዲያን ዘገባ ከሆነ “ከእኛ ዜጎቻችን አንዱ ጥፋት እየፈፀመ ከሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ አንድ ነገር ማድረግ አለብን” ማለታቸውን አስነብቧል። “የውጭ ሀገራት መንግስታትን መጥፎ ባህሪን ማስቆም ባንችል እንኳን ቢያንስ በዜጎቻችን የሚፈፀሙ መጥፎ ባህሪን ልናቆም እንችላለን” ሲሉ አክለዋል።

በሌላ በኩል እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ባለፉት 24 ሰዓታት በፈፀመችው ጥቃት ቢያንስ 57 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 137 ሰዎች ቆስለዋል ሲል የጋዛ የመንግስት ሚዲያ ጽህፈት ቤት ባወጣው ዘገባ አስታውቋል። እ.ኤ.አ. መጋቢት 18 ቀን እስራኤል በጋዛ ላይ ዳግም ጥቃቷን ከቀጠለች በኋላ የሟቾች ቁጥር 1,391 ሲደርስ 3,434 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል። ከጥቅምት 7 ቀን 2023 ጀምሮ ያለው አጠቃላይ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር አሁን ላይ 50,752 ሲደርስ 115 ሺ 475 ያህል ሰዎች ቆስለዋል።

@ዳጉ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...