ሕወሃት በድጋሚ ሊያገረሽ ይችላል ላለው ቀውስ ዓለማቀፍ ጥሪ አቀረበ

Date:

ሕወሃት በትግራይ ክልል በድጋሚ ሊቀሰቀስ የሚችለውን አስከፊ ጦርነት ለማስቆም ዲፕሎማቶችና አጋር አገራት አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቀረበ።

ድርጅቱ ለዓለማቀፉ ኅብረተሰብ በጽሁፍ ባስተላለፈው መልዕክት፣ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የተፈራረሙትን ሁለቱን ወገኖች ወደ ጠረጴዛ ለማምጣት ንቁ ሚና እንዲጫወቱ የጠየቀ ሲሆን፣ እራሱም ቢሆን ቀውሱን ለመፍታት በሚያስችል ፖለቲካዊ ሂደት ውስጥ ለመሳተፍ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መኾኑን ገልጧል።

ሕወሃት አክሎም፣ ዳግም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚለው ስጋት መላ ምት ሳይሆን እውን ለመኾን የተቃረበና ከተከሰተም ቀጠናዊ የመሆን እድሉ ከፍተኛ መሆኑን አስጠንቅቋል።

የመከላከያ ሠራዊት የትግራይን ድንበሮች መክበቡ በሕዝቡ ዘንድ ከባድ ጭንቀት መፍጠሩን የገለጸው ሕወሃት፣ በምዕራብ ትግራይ ያለው “ሕገወጥ” አስተዳደርና በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የፌደራል መንግሥቱ አጋሮች ከፍተኛ የሰብዓዊ መብቶች ጥሠቶችን መፈጸም መቀጠላቸውንና አዳዲስ መፈናቀሎችም እያጋጠሙ መሆኑን ከስሷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...