​ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ኢትዮጵያ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲዋን እንድትቀጥል አሳሰበ

Date:

አይኤምኤፍ እና ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ የሚያስገኘውን የባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ ደረሱ

​ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት እያጋጠማት ያለውን ተለዋዋጭና አሳሳቢ የዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ሁኔታ ለመቋቋም እና የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ስትል፣ የጀመረችውን ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ አጠናክራ እንድትቀጥል በጥብቅ አሳሰበ።

ይህ ማሳሰቢያ የወጣው በኢትዮጵያ መንግሥትና በአይ ኤም ኤፍ የባለሙያዎች ቡድን መካከል በተደረገው የ4 ዓመቱ የተራዘመ የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ ስምምነት መደረሱን ተከትሎ ነው።

ይህ በቅርቡ በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ስምምነት፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ የሚያስችላት ሲሆን፣ ይህም የሀገሪቱን አጠቃላይ የብድር አቅርቦት ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ያደርገዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...