በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ፌስቡክ ገጽ ለኢንቨስተሮች የሚከተለው መልእክት ተላልፏል።
“በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳችን አማካኝነት፣ ግልጽ በሆነ የቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንት ማዕቀፍ፣ በዘመናዊ ልዩ የኢኮኖሚ ቀጠናዎች፣ እንዲሁም ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና እና ለዓለም አቀፍ ገበያዎች ምቹ በሆነ ተደራሽነት ላይ የተመሠረተ፣ ለባለሀብቶች ቅድሚያ የሚሰጥ ምህዳር ገንብተናል።
“በስትራቴጂካዊና በዘላቂነት ላይ ባተኮረ አመራር የሚመራውና በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሚታገዘው የሀገራችን የኢነርጂ አቅርቦት 98% እና ከዚያ በላይ ታዳሽ ሲሆን፤ እየተስፋፋ ያለው ዲጂታል መሰረተ ልማት፣ የተሻሻለው የቴሌኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል በግብርና ቴክኖሎጂ (agritech)፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በፋይናንስ ቴክኖሎጂ፣ በኢ-ኮሜርስ፣ በማዕድን እና በሌሎችም ዘርፎች ዘላቂ ትርፍ ለማስመዝገብ ዝግጁ ናቸው። ይህም ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶችን በማጠናከር የአፍሪካን የጋራ ብልጽግና ያሳድጋል።”
