መጋቢት 5 የጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ ልደታቸው ነው። ጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ማን ናቸው? ለምትሉ “አክሊሉ” የሚል በህይወት ታሪካቸው ላይ የተመሰረተ ታሪካዊ ልቦለድ መጽሐፌን አዘጋጅቻለሁ።
በልደታቸው ቀን ከቀኑ በ8 ሰዓት በብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት በሚገኘው የታሪክ አደራ አዳራሽ 9ኛ ፎቅ እጠብቃችኋለሁ። የምታውቋቸውም ተጋብዛችኋል።
ኑ ታሪካችንን እየሰማን የጀግናችንን ልደት እናክብር። ግብዣዬን ለወዳጅ ዘመዶቻቸሁ አጋሩልኝ። ሰላማዊት ታደሰ
