ሩሲያ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ካልተቀበለች አሜሪካ ራሷን ከድርድሩ ታገላለች

Date:

ሩሲያ የተኩስ አቁም ስምምነቱን የማትቀበል ከሆነ አሜሪካ ራሷን ከድርድሩ እንደምታገል አስታውቃለች፡፡

አሜሪካ፣ ሩሲያ የ30 ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነቱን የምትገፋ ከሆነ ሀገሪቱ ላይ ማዕቀብ እንደምትጥልም አስጠንቅቃለች፡፡

ትራምፕ በዩክሬን የተኩስ አቁም ጉዳይ ላይ ፑቲን ቁርጥ ውሳኔያቸውን እንዲያሳውቁ የሁለት ሳምንት ቀነ ገደብ ሰጥቻለሁ ማለታቸው ይታወሳል፡፡

ትራምፕ እና ፑቲን ካደረጉት የስልክ ውይይት በኃላ ሩሲያ የስምምነት ሰነድ አለማቅረቧ በአሜሪካ ዘንድ የቁርጠኝነት ማነስ ተደርጎ ተቆጥሯል፡፡

ክሬምሊን በበኩሉ በመጪው ሰኞ በኢስታንቡል ለሚካሄደው የሰላም ድርድር የዩክሬንን ምላሽ እየጠበቅኩኝ ነው ብሏል፡፡

ዩክሬን ለተጋበዘችበት 2ኛ ዙር የሰላም ድርድር እስካሁን መስል አለመስጠቷንም ስካይ ኒውስ ዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚገኙ ዜጎቿ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ አስተላለፈች

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ አዳዲስ ወታደራዊ ጥቃቶች ሊሰነዘሩ...

ፍትህ ተሰውቶ የጉልበት ብልጫ የገነነበት ውሳኔ ነው

ለኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች የክፍያ ስርዓት መመሪያ (Financial...

“ተፅዕኖ ፈጣሪዎች” የተባሉ ግለሰቦች በምክክሩ እንዲሳተፉ በምን መስፈረት ተመረጡ?

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 17ኛ ቀን ውሎ የክልል ተወካዮች ጉባኤ...

የአሜሪካ ጦር እስራኤልን ከኢራን መከላከሌን ላቆም እችላለሁ አለ

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት በዚህ...