“ስምምነት ላይ እንደርሳለን አልያም የጀመርነውን እንጨርሳለን”- ትራምፕ

Date:

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር “ስምምነት ላይ እንደርሳለን አልያም የጀመርነውን ሥራ እንጨርሳለን” ሲሉ አስጠነቀቁ።

ትራምፕ በሰጡት ቃለ ምልልስ የሆርሙዝ ወሽመጥ ቢዘጋም የነዳጅ ዋጋ ብዙም እንዳልጨመረ ተናግረዋል።

“ነዳጅ በብዛት ወስደንባቸዋል። ማንም አላወቀም፤ ይሄ የሆነው በአንድ ወር ተኩል ነው” ብለዋል።

የኢራንን ባሕር ኃይል እና አየር ኃይል ማውደማቸውን በድጋሚ ገልጸዋል።

“መቆጣጠሪያ ሥርዓት እንደሌላቸው አውቀዋል። መቆጣጠሪያ ሥርዓታቸው ስለወደመ በምሽት ዒላማ አድርገናቸዋል” ሲሉም ተናግረዋል።

ትራምፕ “ጉልበተኛው ባሕር ኃይላችን ማንም አይቶት የማያውቅ እገዳ ጥሏል። ለሁለት ወር አንድም መርከብ አላለፈም። ለስምምነት ስንቃረብ እገዳውን አላልተናል። ስምምነት ላይ እንደርስ ይሆናል” ሲሉም አክለዋል።

“ዞሮ ዞሮ እናሸንፋለን። ወይ እንስማማለን ወይም ሥራውን እንጨርሳለን” ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

91 ሚሊዮን የኢራን ሕዝብ “እንዲጎዳ ስለማይፈልጉ” ስምምነት ላይ መድረስን እንደሚመርጡ ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጉምሩክ ኮሚሽን ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን ገለጸ

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት 725.25 ቢሊዮን ብር...

ከ1.5 ሚሊዮን ዶላር የአፍሪካ ንፁህ ኢነርጂ ፈንድ አምስቱ አቅኚ የኢትዮጵያ ድርጅቶች ተመረጡ

በምስራቅ አፍሪካ የንፁህ ኢነርጂ አቅርቦትን በማሳደግ የስራ እድልን ለመፍጠርና...

ታላቅ የምስጋና እና የስጦታ መርሃ-ግብር ጥሪ!

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ባለፉት 5 ዓመታት ላበረከቱት ከፍተኛና ታላቅ...

የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ተቀበሩ

ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ላይ የገደሏቸዉ የኢራን...