ስንቄ ባንክ  5 ቢሊየን ብር ማትረፉን ተናገረ

Date:



ጠቅላላ ገቢዬም 15.4 ቢሊዮን ብር ነው ብሏል፡፡

በዚህም ባንኩ የ173 በመቶ እድገት ማሳየቱ አስረድቷል፡፡

ባንኩ ይህንን ያለው የ2024/25 የበጀት ዓመት የስራ አፈጻጸሙን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሀን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።

በተጨማሪም ባንኩ ለኢኮኖሚ ዘርፎች ማለትም ለግብርና፣ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች፣ ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች እንዲሁም ለሴቶች የሰጠሁት ጠቅላላ ብድር መጠን የባንክ ለባንክ ብድርን ሳይጨምር 56.7 ቢሊየን ብር ነው ብሏል።

ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር የ102 በመቶ ጭማሬ ማሳየቱን የተናገረው ስንቄ ባንክ ይህ የብድር መጠን ባንኩ ስራ ከጀመረበት የመጀመሪያው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ218 በመቶ እድገት አሳይቷል ተብሏል።

በመደበኛ የባንክና ማይክሮ ፋይናንስ አገልግሎት ከሚሰጠው ብድር በተጨማሪ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ተግባራዊ አደረኩት ባለው ገቢ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎት በኩል ያለ ምንም ማስያዣ ባለፉት ሁለት ወራት ብቻ ከ240,000 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች 1.2 ቢሊዮን ብር ብድር አቅርቤያለሁ ሲልም አስረድቷል

የባንኩ ጠቅላላ ካፒታል መጠን ባሳለፍነው በጀት ዓመት ከነበረበት 9.7 ቢሊዮን ብር የ2.7 ቢሊዮን ብር ወይም የ28 በመቶ እድገት ማስመዝገቡ የተነገረለት ሲሆን ጠቅላላ ተቀማጩ ደግሞ 102.5 ብር ደርሷል ሲል ባንኩ ተናግሯል።

590 ቅርንጫፎች እንዳሉትም ባንኩ ጠቅሷል፡፡

81 በመቶ የሚሆነው የባንኩ ቅርንጫፎች የሚገኙት በገጠሪቱ የሀገሪቱ አካባቢ መሆኑም ሲነገር ሰምተናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...

በኢትዮጵያ በማሳደጊያ ተቋማት የሚገኙ ሕፃናት ቁጥር ወደ 12 ሺሕ ዝቅ አለ

በኢትዮጵያ በተለያዩ የሕፃናት ማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ሕፃናት...