በረሀብ እና በአልሚ ምግብ እጥረት ምክንያት የሞቱ ተፈናቃዮች ቁጥር 992 መድረሱ ተነገረ

Date:

በትግራይ ክልል በሽሬ ከተማ በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ከሚገኙ ተፈናቃዮች መካከል በአልሚ ምግብ እጥረት እና በርሃብ ምክንያት የሞቱት ተፈናቃዮች ቁጥር 992 መድረሱን የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ጸሐዬ እምባዬ በ1 ዓመት ጊዜ ውስጥ የደረሰው ሰብአዊ ኪሳራ ተጠንቶ መጠናቀቁን እና ቁጥሩም ከ550 ወደ 992 ከፍ ማለቱን  ተናግረዋል። 

በአሁኑ ሰዓት በሽሬ ከተማ እና በአካባቢዋ ከ250 ሺሕ በላይ ተፈናቃይ በርሃብና በሽታ እየተሰቃዩ መሆኑን አንስተው፤ የሚመለከተው አካል ትኩረት እንዲሰጣቸው ጥሪ አቅርበዋል።

በሽሬ ከተማ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በክልሉ የሚገኙት ተፈናቃዮቹ በ2015 ዓ.ም. ጥር ወር አካባቢ ጀምሮ የሚሰጣቸው ሰብአዊ እርዳታ በመቋረጡ ምክንያት፤ ተፈናቃዮች ለርሃብ እና ለበሽታ መዳረጋቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) ለእያንዳንዱ ተፈናቃይ 15 ኪ.ግ. ዱቄት እርዳታ እንደሚሰጥ ቢያሳውቅም እየተሰጠ ያለው ግን 9 ኪ.ግ. መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፤ የሚላከው የእርዳታ እህል ከሚያስፈልገው ጋር ልዩነት አለው” ብለዋል።

በአጠቃላይ በትግራይ ክልል ከሱዳን የተመለሱ እና ወደ ቀያቸው ተመልሰው በጸጥታ ችግር ምክንያት IDP በተባለ ተቋም ሥር ያሉትን ሳይጨምር 970 ሺሕ በላይ ተፈናቃዮች በችግር ውስጥ መሆናውን ኃላፊው አስታውቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...