በሱዳን የጤናው ዘርፍ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ

Date:

በሱዳን እየተካሄደ ያለው ደም አፋሳሽ ጦርነት የሀገሪቱን የጤና ሥርዓት ክፉኛ በመጉዳቱ፣ ለተላላፊ በሽታዎች መስፋፋት ዋነኛ መንስኤ መሆኑ ተገለጸ።

የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፣ በአሁኑ ወቅት የዴንጊ ትኩሳት፣ የወባ፣ የኩፍኝ እና የሄፓታይተስ ኢ ወረርሽኞች በተለያዩ ግዛቶች በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጩ ይገኛሉ።

በተለይም በዴንጊ ትኩሳት የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ 7 ሺህ የተቃረበ ሲሆን፣ የሟቾች ቁጥርም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ጭማሪ አሳይቷል።

የመሠረተ ልማት መውደም፣ የመንገዶች መዘጋት እና የሎጂስቲክስ መስተጓጎል የሕይወት አድን መድኃኒቶች ለታካሚዎች እንዳይደርሱ ትልቅ እንቅፋት ፈጥሯል።

ከዚህም በተጨማሪ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ከመኖሪያ ቀያቸው መፈናቀላቸው በየክልሎቹ የሚገኙ ጥቂት ሆስፒታሎች ከአቅማቸው በላይ እንዲወጠሩ አድርጓቸዋል።

ሚኒስቴሩ ችግሩን ለመቅረፍ የድንገተኛ አደጋ ማዕከላትን በማንቀሳቀስና ለተፈናቃይ ቤተሰቦች የሕክምና ቁሳቁስ ለማድረስ ጥረት እያደረገ ቢሆንም፣ የጦርነቱ መቀጠል ለጤና ባለሙያዎች ፈታኝ ሆኖባቸዋል።

ይህ ቀውስ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን የሰብአዊ መብት ረገጣ እና የጤና ስጋት ይበልጥ አሳሳቢ ደረጃ ላይ አድርሶታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...