በበርበራ እና በአዲስ አበባ መካከል ቀጥታ በረራ በቅርቡ እንደሚጀመር ተጠቆመ

Date:

የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ የበርበራ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ጎብኝተዋል። በዚህ ወቅትም አየር ማረፊያው አሁን ላይ ለዓለም አቀፍ ንግድ ክፍት መሆኑን መሆኑ ተገልጿል።

የሶማሊላንድ የአቬሽን ሚኒስትሩ ፉአድ አህመድ ኑኡስ በበርበራ እና በአዲስ አበባ መካከል የካርጎ እና የመንገደኞች በረራ በቅርቡ እንደሚጀመር አረጋግጠዋል።

በዚህም በርበራን ከአዲስ አበባ ጋር በማስተሳሰር ሶማሊላንድ፥ የዓሳ እና ሌሎች ምርቶች በበርበራ ኤርፖርት ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ ያስችላታል ተብሏል።

በአዲስ አበባ እና በርበራ መካከል የሚደረገውን ጉዞ ቀላል በማድረግ የንግድ እና ቱሪዝምን እድገቱን ለማስፋትም ታቅዷል።

ዘገባው የሶማሊላንድ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...