በትግራይ አስገድዶ መሰወርና ከሕግ ውጭ እስር ተንሰራፍቷል

Date:

“ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች” የተሰኘው ተቋም በትግራይ ክልል ውስጥ “አስገድዶ መሠወር” እና “ከሕግ ውጭ የኾነ እስር” በስፋት መንሰራፋቱን  በማሳወቅ ከፍተኛ ስጋቱን ገልጿል።

የመንግሥት አካላት ለሚፈጸሙት ጥሰቶች ኃላፊነት የማይወስዱበትና ተጠያቂነት የሌለበት ሁኔታ መስፈኑን የጠቀሰው ተቋሙ፣ ይህም በክልሉ ያለውን የፍትህ ሥርዓት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ጥሎታል ብሏል።

በተለይም ጋዜጠኞችና የፖለቲካ አስተያየት ሰጪዎች የሐሳብ ነፃነታቸውን በመጠቀማቸው ብቻ የዛቻና የማስፈራሪያ ዒላማ እየሆኑ መምጣቸው ተመላክቷል። ባለሥልጣናት በነፃነት ሐሳባቸውን በሚገልጹ ዜጎች ላይ የሚያደርሱትን ወከባ በአስቸኳይ እንዲያቆሙ ተቋሙ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

ተቋሙ በመጨረሻም የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ያሉበት ባልታወቁ ሰዎች ዙሪያ ሙሉ መረጃ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል። በተጨማሪም በተሰወሩ ግለሰቦች ላይ “ገለልተኛ”፣ “ግልጽ” እና “አፋጣኝ” ምርመራ ተካሂዶ ውጤቱ ለሕዝብ ይፋ እንዲሆን በጽኑ ጠይቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...