በአሜሪካ በጭነት አውሮፕላን መከስከስ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ

Date:

በአሜሪካ ኬንታኪ ግዛት ትናንት ምሽት በደረሰ የዩፒኤስ ጭነት አውሮፕላን መከስከስ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡

የጭነት አውሮፕላኑ ከሉዊስቪል ሙሐመድ አሊ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መብረር በጀመረ ጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ መከስከሱ ተመላክቷል፡፡

የኬንታኪ ግዛት አስተዳዳሪ አንዲ በሺዬር÷ የጭነት አውሮፕላኑ ከተነሳ በኋላ ብዙም ሳይቆይ የመፈንዳት አደጋ እንዳጋጠመው አስረድተዋል፡፡

በተከሰተው አደጋም እስካሁን የ7 ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን ÷11 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን አመልክተዋል፡፡
የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል ጠቁመው÷ የአደጋውን መንስኤ ለማወቅ ምርመራ እየተካሄደ ይገኛል ነው ያሉት፡፡

አደጋውን ተከትሎ የተፈጠረውን የእሳት አደጋ በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን ገልጸዋል፡፡
የበረራ ቁጥሩ 2979 የሆነው የጭነት አውሮፕላን 38 ሺህ ጋሎን ነዳጅ ጭኖ ወደ ሆኖሉሉ ሊያቀና እንደነበር ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...