በኢትዮጵያ እና ሩሲያ መካከል ያለው የንግድ ፍሰት ጨመረ

Date:

የሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ ማክሲም ሬሽትኒኮቭ ከኢትዮጵያ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ ጋር በቪዲዮ ኮንፍረንስ ተወያይተዋል።

ሁለቱ ሚኒስትሮች በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን ትብብር እና አጋርነት ለማጠናከር ስለሚያስችሉ ጉዳዮች መምከራቸው ተዘግቧል።

እንደ ሩሲያው የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለው የንግድ ፍሰት እየጨመረ ሲሆን ባለፈው አመት ከነበረው አንፃር በዘንድሮ ስድስት ወራት ያለው የንግድ ፍሰት ከሁለት እጥፍ በላይ ጨምሯል።

ባለፉት ስድስት ወራት በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለው የንግድ ፍሰት 191 ሚሊየን ዶላር ተሻግሯል ያሉት ሚኒስትሩ ለዚህ የንግድ ፍሰት መጨመር ምክንያቱ በዋነኝነት ሃገራቸው ከኢትዮጵያ የምታስገባው የቡና ምርት መጨመር መሆኑን አንስተዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም የሩሲያ አምራቾች ማዳበሪያ እና የግብርና ማሽኖችን ለኢትዮጵያ ለማቅረብ ዝግጁ መሆናቸውን አንስተዋል።

tikvahethmagazine

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...