በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

Date:

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ሲ ቫይረስ ጋር እንደሚኖሩ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በተቋሙ የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ፍቃዱ የዴታ እንደገለጹት፣ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ባካሄደው ጥናት የሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ አጠቃላይ ብሔራዊ የስርጭት መጠን ከ5.7 እስከ 6.9 በመቶ አካባቢ መሆኑ ተረጋግጧል።

ይህ ስርጭት መካከለኛ እና ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ በመሆኑ፣ ሀገሪቱ በዓለም የጤና ድርጅት መሥፈርት መሠረት ቫይረሱ በስፋት ከሚታይባቸው ቀጠናዎች ተርታ እንድትገኝ አድርጓታል።

ለ16ኛ ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሄፓታይተስ ቀን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ማከናወኑን ዶክተር ፍቃዱ አንስተዋል።

በሽታው መጀመሪያ ላይ ምንም ዓይነት ምልክት ሳያሳይ የሚቆይ ዝምተኛ ገዳይ በመሆኑ፣ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያስተላልፉ አድርጓቸዋል ብለዋል።

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በሽታውን በ2030 ከወረርሽኝ ደረጃ ለማውረድ እየሠራ መሆኑን ገልጸው፣ አዲስ የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር 90 በመቶ ለመቀነስ ማቀዱን ተናግረዋል።

ለአሐዱ ሬዲዮ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና...

ኢራንን ለመምታት የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከምድሯ ይነሱ እንደነበር እሥራኤል ይፋ አደረገች

የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች...

በጋምቤላ ክልል በጀት ዓመት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ2 ቢሊዮን በላይ ጭማሪ አሳየ

 በጋምቤላ ክልል በበጀት አመቱ በተከናወነው የገቢ አሰባሰብ ዙሪያ የተሻለ...

አቶ ዓለማየሁ ጢሞቴዎስ የ10 ዓመት እስራት ተፈረደባቸው

‎‎የሲዳማ ክልል ፍትሕ ቢሮ እንዳስታወቀው የቀድሞ የሲዳማ ክልል ሰላም...