በኢትዮጵያ በአሁን ሰአት የከባድ የአዕምሮ ህመም 0 ነጥብ 6 በመቶ እንደሚደርስና ይህም ማለት ከ1 ሺህ ሰው ውስጥ ወደ 5 የሚደርሱ ሰዎች ላይ እንደሚከሰት ተገለጿል::
ይህ የተገለፀው ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በዛሬው እለት ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር ባካሄደው ውይይት ላይ ነው::
በውይይቱ ላይ በ ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የአዕምሮ ህክምና ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር እስጢፋኖስ እንዳለማው እንደገለጹት የአዕምሮ ህመምን ለማከም የተለያየ የህክምና አማራጭ ያለ ሲሆን በተለያየ የህክምና መንገድ እንዲድን ማድረግ ይቻላል:
ዶ/ር እስጢፋኖስ አክለውም በኢትዮጵያ የድብርት ህመሞች 9 በመቶ እንደሚደርሱ ገልጸዋል::
ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በአሁን ሰዓት የአዕምሮ ህመም ህክምናን ከሌሎች ህክምናዎች ጋር በማቀናጀት እየሰራ እንደሚገኝና 145 የሚደርሱ የአዕምሮ ህመም ታካሚን አስተኝቶ ለማሳከም የሚያስችሉ አልጋዎች እንዳሉት ተጠቁሟል::
ሆስፒታሉ የሚሰጠውን የህክምና አገልግሎት በተሻለ መልኩ ለማከናወን የእድሳትና የማስፋፊያ ስራ እያካሄደ እንደሚገኝ ተገልጾ እድሳቱ እየተከናወነ የሚገኘው በጤና ሚኒስቴር እንደሆነና 185 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እንደሆነም ተነግሯል:: ይህም እድሳት ሆስፒታሉ አገልግሎቱን በደንብ እንዲሻሻል ያደርጋል ተብሏል::
የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ የኒውሮ ሳይንስ ኢንስቲትዩት ለመሆን እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል:
