በኢትዮጵያ የከባድ የአዕምሮ ህመም 0 ነጥብ 6 በመቶ እንደሚደርስ ተገለጸ

Date:

በኢትዮጵያ በአሁን ሰአት የከባድ የአዕምሮ ህመም 0 ነጥብ 6 በመቶ እንደሚደርስና ይህም ማለት ከ1 ሺህ ሰው ውስጥ ወደ 5 የሚደርሱ ሰዎች ላይ እንደሚከሰት ተገለጿል::

ይህ የተገለፀው ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በዛሬው እለት ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር ባካሄደው ውይይት ላይ ነው::

በውይይቱ ላይ በ ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የአዕምሮ ህክምና ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር እስጢፋኖስ እንዳለማው እንደገለጹት የአዕምሮ ህመምን ለማከም የተለያየ የህክምና አማራጭ ያለ ሲሆን በተለያየ የህክምና መንገድ እንዲድን ማድረግ ይቻላል:

ዶ/ር እስጢፋኖስ አክለውም በኢትዮጵያ የድብርት ህመሞች 9 በመቶ እንደሚደርሱ ገልጸዋል::

ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በአሁን ሰዓት የአዕምሮ ህመም ህክምናን ከሌሎች ህክምናዎች ጋር በማቀናጀት እየሰራ እንደሚገኝና 145 የሚደርሱ የአዕምሮ ህመም ታካሚን አስተኝቶ ለማሳከም የሚያስችሉ አልጋዎች እንዳሉት ተጠቁሟል::

ሆስፒታሉ የሚሰጠውን የህክምና አገልግሎት በተሻለ መልኩ ለማከናወን የእድሳትና የማስፋፊያ ስራ እያካሄደ እንደሚገኝ ተገልጾ እድሳቱ እየተከናወነ የሚገኘው በጤና ሚኒስቴር እንደሆነና 185 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እንደሆነም ተነግሯል:: ይህም እድሳት ሆስፒታሉ አገልግሎቱን በደንብ እንዲሻሻል ያደርጋል ተብሏል::

የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ የኒውሮ ሳይንስ ኢንስቲትዩት ለመሆን እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል:

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ መስከረም 9 2019 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

-የግዮን እንግዳ አምዳችን :- ‹‹ምንጩና ጸሐፊው በማይታወቅ መረጃ መመራት አደገኛ...

ሸኽ መሃመድ አል አሙዲ ተጨማሪ 40 ሺህ ሠራተኞች እንዲቀጠሩ አቅጣጫ ሰጡ

የMIDROC Investment Group ሊቀመንበር ሼክ መሃመድ ሁሴን አል...

የወርቅ ማዕድን ሠራተኛው ከመገደላቸው በፊት ቤተሰባቸው ከታጣቂዎች ጋር ያደረገው የመጨረሻው የስልክ ምልልስ

ማስጠንቀቂያ፡ ቀጥሎ የሚያነብቡት ታሪክ ሊረብሽዎት ይችላል በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ...