በኢትዮጵያ የክፍያ ስርዓት የተከፈለ ካፒታል ወደ 100 ሚሊዮን ብር ከፍ ተደረገ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዲጂታል ክፍያዎችን እና የፋይናንስ ተደራሽነትን ለማሳደግ የክፍያ ስርዓት መመሪያውን ማሻሻሉን አስታዉቋል።

ማዕከላዊ ባንኩ “የክፍያ መፈጸሚያ ሰነድ አውጪዎች ፈቃድ እና እውቅና አሰጣጥ መመሪያውን” ያሻሻለ ሲሆን በዘርፉ ፍቃድ ለመዉሰድ ይጠይቅ የነበረዉ 50 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል አሁን ወደ 100 ሚሊዮን ብር ከፍ ብሏል።

በሥራ ላይ የዋለው አዲሱ መመሪያ ቁጥር ONPS/10/2025፣ አሁን ፈቃድ ያላቸው የክፍያ ሥርዓት ኦፐሬተሮች ካፒታላቸው ከዚህ መጠን በታች ከሆነ እኤአ እስከ ሰኔ 2027 መጨረሻ ድረስ ይህንን መስፈርት እንዲያሟሉ ተጠይቀዋል።

በፈቃድ አሰጣጥ ሂደት ላይ ያሉ ደግሞ ፈቃዳቸውን ከተቀበሉ በሁለት ዓመት ውስጥ አዲሱን የካፒታል እና የአክሲዮን ድርሻ መስፈርቶች ማሟላት እንደሚጠበቅባቸው ካፒታል ለመረዳት ችሏል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...