በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር የሥራ ጉብኝት አደረጉ

Date:

በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ክቡር ሱን ክሮግስትረፕ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።

አምባሳደሩ በፍርድ ቤቱ ያለውን የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን፣ የዳኝነት ሥርዓቱን ግልጽነትና ተጠያቂነት ለማስፈን እየተከናወነ ያለው የዲጂታላይዜሽን ሥራ የሚደነቅ እመርታ መሆኑን ገልጸዋል።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በበኩላቸው፣ የዴንማርክ የሰብዓዊ መብቶች ተቋም ለኢትዮጵያ ዳኞች ለሰጠው የሙያ ሥልጠና ምስጋና አቅርበው፤ በሁለቱ አገራት መካከል ያለው ግንኙነት በፍትሕ ዘርፉ ይበልጥ እንዲጠናከር ፍላጎታቸውን ገልጸዋል።

አምባሳደር ሱን ክሮግስትረፕም ዴንማርክ ከኢትዮጵያ የፍትሕ አካላት ጋር ያላትን አጋርነት አጠናክራ ለመቀጠል ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።

ይህ ጉብኝት በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...