በኢንዱስትሪ ፓርክ ሁለት ሠራተኞች ሞቱ

Date:

በሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ በደረሰ አደጋ ሁለት ሠራተኞች ሞቱ
በሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ በደረሰ የማሽን ፍንዳታ አደጋ ሁለት ሠራተኞች ወዲያውኑ ሲሞቱ ሌሎች ሁለት ሰዎች ቀሰሉ ፡፡

አደጋው በፓርኩ ከሚገኙ የምርት ማዕከላት መካከል በአንደኛው ውስጥ ትናንት መድረሱን የፓርኩ የሥራ ሃላፊ አስታውቀዋል ፡፡ አደጋው ሊደርስ የቻለው በምርት ክፍሉ ውስጥ የሚገኘው ማሞቂያ በመፈንዳቱ መሆኑን የፓርኩ ዋና ሥራ ሥራአስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አሸናፊ ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል ፡፡

በአደጋው የሁለት ሠራተኞች ህይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ ጉዳት የደረሰባቸው ሌሎች ሁለት ሰዎች ደግሞ በሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና ዕርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ አቶ ማቴዎስ ተናግረዋል ፡፡


ዶቼ ቬሌ ያነጋገራቸው የሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል አስተዳዳሪ አቶ ዝናው ሳርሚሶ በበኩላቸው ትናንት ሁለት ሰዎች በእሳት ቃጠሉ ተጎድተው ወደ ሆስፒታል መድረሳቸውን አረጋግጠዋል ፡፡ ተጎጂዎቹ አንደኛው ከባድ ሌላኛው ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑን የጠቀሱት የሆስፒታሉ ዋና አስተዳዳሪ “ አሁን የህክምና ዕርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል “ ብለዋል ፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...

ሕወሓት ድብረጺዮንን የክልሉ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ

የክልሉ ፕሬዚዳንት ተደርገው የተመረጡት  ድብርጺዮን ገ/ ሚካዔል (ዶ/ር)  ቃለ...

” ኢራን ከምድረ ገጽ ትጠፋለች ” – ትራምፕ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፎክስ ኒውስ ቴሌቪዥን ጋር ቃለ...

የአርበኞች ድል መታሰቢያ እና የዛሬው ትውልድ ለሕብረት ያለው አቋም

የጥንት ኢትዮጵያዊያንአርበኞች ድል 85 ኛው ዓመት መታሰቢያ ሚያዚያ...