የኢትዮጵያ መንግሥት ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር የ3.5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ ሽግሽግ ስምምነት ተፈራረመ

Date:

የኢትዮጵያ መንግሥት በቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ የዕዳ ሽግሽግ ስር ከኢትዮጵያ ኦፊሴላዊ አበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር የዕዳ ሽግሽግ የመግባቢያ ሰነድ ላይ ከስምምነት መድረሱን የገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል።

ስምምነቱ እ.አ.አ ማርች 2025 በመርሕ ደረጃ የተደረሰውን የብድር ሽግሽግ በይፋ ተግባራዊ የሚያደርግ እና ለሀገሪቱ የ3.5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ዕዳ የክፍያ እፎይታ የሚሰጥ መሆኑ ተጠቁሟል።

ይህም ለዓመታት ሲደረግ ለነበረው ድርድር ስኬታማ መቋጫ ከመሆኑም ባሻገር ኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ የመንግሥት ዕዳ ዘላቂነትን ለማረጋገጥ ለምታደርገው ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ እንደሆነ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ገልጿል።

የመግባቢያ ሰነዱ ከተፈረመ በኋላ ስምምነቱ ከእያንዳንዱ የኮሚቴው አባላት ጋር በሚደረጉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች አማካኝነት ተግባራዊ ይሆናል።

የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ ስምምነቱን በማስመልከት በሰጡት መግለጫ፤ “በእስካሁኑ ሂደት የተንፀባረቀው የትብብር መንፈስ በሁለትዮሽ ስምምነቶች ሂደት ወቅትም እንደሚቀጥል እና ሂደቱን ለማፋጠን እንደሚረዳ የጸና እምነት አለን” ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከውጭ አበዳሪዎች ጋር በቅን ልቦና መሥራቷን እንደምትቀጥልም ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...