የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር የቀበሌ መታወቂያ እንዳይሰጥና እንዲሰረዝ እንዲሁም በከተማው ማንኛውም አገልግሎት የሚሰጠው በብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ብቻ መሆኑን አስታውቋል።
ከዛሬ ጀምሮ ሁሉም ሰው በብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ብቻ እንዲጠቀምና በከተማው በሁሉም ቀበሌያት መደበኛ መታወቂያ እንዳይሰጥና እንዲሰረዝ ነው አስተዳደር ምክር ቤቱ የወሰነው።
ከተማ አስተዳደሩ በከተማው የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ተግባራትና ወንጀሎች ለመከላከል በማሰብ ለማንኛውም ዓይነት አገልግሎቶች ህብረተሰቡ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ብቻ እንዲጠቀም አሳስቧል።
በከተማው ባሉ ሁሉም ቀበሌዎች ከዛሬ ጀምሮ መደበኛ መታወቂያ እንደማይሰጥና እንደተሰረዘ ነው የተገለጸው።
ነዋሪዎች እንዲሁም በከተማው የሚንቀሳቀሱ ማንኛውም ግለሰብ ከዚህ በኃላ ምንም ዓይነት የቀበሌ መታወቂያ መጠቀም እንደማይቻልም አጽንኦት ሰጥቶ ገልጿል።
በመሆኑም የመደበኛ መታወቂያ የሰጠ እንዲሁም በመታወቂያው የተጠቀመ ግለሰብ በህግ እንደሚጠየቅም ነው ያሳሰበው።
መረጃው የከተማ አስተዳደሩ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@TikvahethMagazine
