በኢራን ዋና ከተማ የሚገኘው ታሪካዊው እና በዩኔስኮ በቅርስነት የተመዘገበው የጎሌስታን ቤተ መንግሥት በመዲናዋ በተፈጸመው ጥቃት ጉዳት ደረሰበት።
የደረሰውን ጉዳት ተከትሎ ዩኔስኮ ለቅርሶች የሚደረገው ጥበቃ እንዳሳሰበው ገልጿል።
የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከቤተ መንግሥቱ አቅራቢያ አርግ አደባባይ ላይ ፍንዳታ ተከስቷል።
የጎሌስታን ቤተ መንግሥት በቃጃር ስርወ መንግሥት ዘመን የኢራን ንጉሳውያን ቤተሰቦች መኖሪያ የነበረ ሲሆን በኋላ ላይ ደግሞ የፓህላቪ ስርወ መንግሥት ዋና መኖሪያ ነበር።
