እስራኤል በቴህራን የፕሬዝዳንቱን ፅሕፈት ቤት ደበደበች

Date:

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በተሸጋገረበት በዚህ ወቅት፥እስራኤል በኢራን መዲና ቴህራን በሚገኘው “የመሪዎች ቅጥር ግቢ” እና በፕሬዝዳንቱ ፅሕፈት ቤት ላይ ጥቃት መፈጸሟን አስታውቃለች።

ከቅዳሜ ጀምሮ በቴህራን “እያንዳንዱ የከተማዋ ክፍል” ጥቃት እየደረሰበት መሆኑን የዐይን እማኞች እየገለጹ ነው።

አዳዲስ የወጡ ምስሎችም በከተማዋ ምስራቃዊ አቅጣጫ ግዙፍ ፍንዳታዎች መከሰታቸውን ያሳያሉ።

የቀይ ጨረቃ ባወጣው መረጃ መሠረት፥ የአሜሪካና የእስራኤል ጥቃት ከተጀመረ ወዲህ በኢራን የሟቾች ቁጥር 7መቶ87 ደርሷል።

በሳውዲ አረቢያ ሪያድ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከኢራን በተነሱ ሁለት ድሮኖች መመታቱ ተረጋግጧል።

በሌላ ግንባር እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምድር ወረራዋን እንደምታሰፋና “ተጨማሪ ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን ለመቆጣጠር” ወታደሮቿ ወደፊት እንደሚገሰግሱ አስታውቃለች።

ግጭቱን ተከትሎ የዓለም አቀፍ የጋዝ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እየናረ ይገኛል።

ሰኞ ዕለት የ50 በመቶ ጭማሪ የታየ ሲሆን፥ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት ደግሞ ተጨማሪ የ30 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...