በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በተሸጋገረበት በዚህ ወቅት፥እስራኤል በኢራን መዲና ቴህራን በሚገኘው “የመሪዎች ቅጥር ግቢ” እና በፕሬዝዳንቱ ፅሕፈት ቤት ላይ ጥቃት መፈጸሟን አስታውቃለች።
ከቅዳሜ ጀምሮ በቴህራን “እያንዳንዱ የከተማዋ ክፍል” ጥቃት እየደረሰበት መሆኑን የዐይን እማኞች እየገለጹ ነው።
አዳዲስ የወጡ ምስሎችም በከተማዋ ምስራቃዊ አቅጣጫ ግዙፍ ፍንዳታዎች መከሰታቸውን ያሳያሉ።
የቀይ ጨረቃ ባወጣው መረጃ መሠረት፥ የአሜሪካና የእስራኤል ጥቃት ከተጀመረ ወዲህ በኢራን የሟቾች ቁጥር 7መቶ87 ደርሷል።
በሳውዲ አረቢያ ሪያድ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከኢራን በተነሱ ሁለት ድሮኖች መመታቱ ተረጋግጧል።
በሌላ ግንባር እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምድር ወረራዋን እንደምታሰፋና “ተጨማሪ ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን ለመቆጣጠር” ወታደሮቿ ወደፊት እንደሚገሰግሱ አስታውቃለች።
ግጭቱን ተከትሎ የዓለም አቀፍ የጋዝ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እየናረ ይገኛል።
ሰኞ ዕለት የ50 በመቶ ጭማሪ የታየ ሲሆን፥ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት ደግሞ ተጨማሪ የ30 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
