እስራኤል በቴህራን የፕሬዝዳንቱን ፅሕፈት ቤት ደበደበች

Date:

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በተሸጋገረበት በዚህ ወቅት፥እስራኤል በኢራን መዲና ቴህራን በሚገኘው “የመሪዎች ቅጥር ግቢ” እና በፕሬዝዳንቱ ፅሕፈት ቤት ላይ ጥቃት መፈጸሟን አስታውቃለች።

ከቅዳሜ ጀምሮ በቴህራን “እያንዳንዱ የከተማዋ ክፍል” ጥቃት እየደረሰበት መሆኑን የዐይን እማኞች እየገለጹ ነው።

አዳዲስ የወጡ ምስሎችም በከተማዋ ምስራቃዊ አቅጣጫ ግዙፍ ፍንዳታዎች መከሰታቸውን ያሳያሉ።

የቀይ ጨረቃ ባወጣው መረጃ መሠረት፥ የአሜሪካና የእስራኤል ጥቃት ከተጀመረ ወዲህ በኢራን የሟቾች ቁጥር 7መቶ87 ደርሷል።

በሳውዲ አረቢያ ሪያድ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከኢራን በተነሱ ሁለት ድሮኖች መመታቱ ተረጋግጧል።

በሌላ ግንባር እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምድር ወረራዋን እንደምታሰፋና “ተጨማሪ ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን ለመቆጣጠር” ወታደሮቿ ወደፊት እንደሚገሰግሱ አስታውቃለች።

ግጭቱን ተከትሎ የዓለም አቀፍ የጋዝ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እየናረ ይገኛል።

ሰኞ ዕለት የ50 በመቶ ጭማሪ የታየ ሲሆን፥ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት ደግሞ ተጨማሪ የ30 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በአንድ ዓመት ውስጥ ቃል የተገቡ 417 የዓይን ብሌኖች ለሆስፒታሎች ተሰራጩ

​ የኢትዮጵያ የደምና ሕብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት በተጠናቀቀው የ2018 በጀት...

በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው

በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው በኢትዮጵያ...

ትምህርት ሚኒስቴር ለአዲሱ ዓመት 11 አዳዲስ የሙያ ትምህርት ዓይነቶችን ይፋ አደረገ

​የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከክልል...

የአዲስ አበባ ጉዳይ በሌሎች አጀንዳዎች ላይ የሚካሄደውን ምክክር ጥላ አጥሎበታል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በ25ኛ ቀን ውሎው በሥራ ቡድን ደረጃ...